SPORT NEWS: ሌሮይ ሳኔ ከጀርመን የአለም ዋንጫ ስብስብ ውጭ ሆነ – Leroy Sane Left Out of Germany World Cup Squad

የጀርመኑ አሰልጣኝ ዮዓኪም ሎው በ2018ቱ የሩሲያው የአለም ዋንጫ የሚሳተፈውን የመጨረሻ ስብስብ ይፋ አድርገዋል።

በቡድኑ ስብስብ ውስጥ በማንቼስተር ሲቲ በዘንድሮው አመት ጥሩ የውድድር አመት ያሳለፈው የግራ መስመር አማካዩ ሌሮይ ሳኔ ሳይካተት ቀርቷል።

ግብ ጠባቂዎች፦ ማርክ አንደር ቴርስቴገን – ባርሴሎና፣ ኬቪን ትራፕ – ፒ ኤስ ጂ እና ማኑዌል ኑዌር – ባየር ሙኒክ።

ተከላካዮች፦ ማትስ ሃመልስ፣ ጆሹዋ ኪሚች፣ ኒክላስ ሱሌ እና ጀሮም ቦዓቴንግ – ባየር ሙኒክ፣ አንቶኒዮ ሩድሪገር – ቼልሲ፣ ማቲያስ ጊንተር – ቦሩሲያ ሞንቼግላድባህ፣ ማርቪን ፕላቴሃርት – ኸርታ በርሊን እንዲሁም ዮናስ ሄክቶር ከኤፍ ሲ ኮሎኝ ተመርጠዋል።

አማካዮች፦ ቶኒ ክሩስ – ሪያል ማድሪድ፣ ጁሊያን ብራንድት – ባየር ሌቨርኩዘን፣ ጁሊያን ድራክስለር – ፒ ኤስ ጂ፣ ሳሚ ኬዲራ – ጁቬንቱስ፣ ኢካይ ጉንዶጋን – ማንቼስተር ሲቲ፣ ሊዮን ጎርትዝካ – ሻልከ፣ ሜሱት ኦዚል – አርሰናል እንዲሁም ሰባስቲያን ሩዲ ከባየር ሙኒክ ተካተዋል።

አጥቂዎች፦ ቶማስ ሙለር – ባየር ሙኒክ፣ ቲሞ ዌርነር – ረ ቢ ሌፕዚግ፣ ማሪዮ ጎሜዝ ከስቱትጋርት እንዲሁም ማርኮ ሬውስ ከቦሩሲያ ዶርትመንድ የአለም ዋንጫው አባል መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

ምንጭ: ቢቢሲ

Advertisement

1 Comment

Comments are closed.