Deprecated: Required parameter $wrapper follows optional parameter $type in /customers/d/c/1/planetethiopia.com/httpd.www/magazine/wp-content/plugins/featured-images-for-rss-feeds/includes/freemius/includes/class-fs-logger.php on line 145 Warning: Cannot modify header information - headers already sent by (output started at /customers/d/c/1/planetethiopia.com/httpd.www/magazine/wp-content/plugins/featured-images-for-rss-feeds/includes/freemius/includes/class-fs-logger.php:145) in /customers/d/c/1/planetethiopia.com/httpd.www/magazine/wp-content/plugins/onecom-vcache/vcaching.php on line 614 Warning: Cannot modify header information - headers already sent by (output started at /customers/d/c/1/planetethiopia.com/httpd.www/magazine/wp-content/plugins/featured-images-for-rss-feeds/includes/freemius/includes/class-fs-logger.php:145) in /customers/d/c/1/planetethiopia.com/httpd.www/magazine/wp-content/plugins/onecom-vcache/vcaching.php on line 622 Warning: Cannot modify header information - headers already sent by (output started at /customers/d/c/1/planetethiopia.com/httpd.www/magazine/wp-content/plugins/featured-images-for-rss-feeds/includes/freemius/includes/class-fs-logger.php:145) in /customers/d/c/1/planetethiopia.com/httpd.www/magazine/wp-includes/feed-rss2.php on line 8 History | ታሪክ – Planet Ethiopia መጽሔት https://magazine.planetethiopia.com መረጃ | መማሪያ | መዝናኛ ጽሑፎች Wed, 14 Nov 2018 10:09:12 +0000 en-GB hourly 1 https://wordpress.org/?v=6.5.3 https://usercontent.one/wp/magazine.planetethiopia.com/wp-content/uploads/2018/05/cropped-PE-logo-rounded-32x32.png?media=1712435692 History | ታሪክ – Planet Ethiopia መጽሔት https://magazine.planetethiopia.com 32 32 በዓለም አቀፍ ደረጃ በርካታ ሰዎች ያለሀኪም ትዕዛዝ የጸረ ባክቴሪያ መድሃኒቶችን ይወስዳሉ – የዓለም ጤና ድርጅት https://magazine.planetethiopia.com/2018/11/14/%e1%89%a0%e1%8b%93%e1%88%88%e1%88%9d-%e1%8a%a0%e1%89%80%e1%8d%8d-%e1%8b%b0%e1%88%a8%e1%8c%83-%e1%89%a0%e1%88%ad%e1%8a%ab%e1%89%b3-%e1%88%b0%e1%8b%8e%e1%89%bd-%e1%8b%ab%e1%88%88%e1%88%80%e1%8a%aa/ https://magazine.planetethiopia.com/2018/11/14/%e1%89%a0%e1%8b%93%e1%88%88%e1%88%9d-%e1%8a%a0%e1%89%80%e1%8d%8d-%e1%8b%b0%e1%88%a8%e1%8c%83-%e1%89%a0%e1%88%ad%e1%8a%ab%e1%89%b3-%e1%88%b0%e1%8b%8e%e1%89%bd-%e1%8b%ab%e1%88%88%e1%88%80%e1%8a%aa/#comments Wed, 14 Nov 2018 10:09:12 +0000 http://magazine.planetethiopia.com/?p=6616 ዓለም አቀፍ ደረጃ በርካታ ሰዎች ያለሀኪም ትዕዛዝ የጸረ ባክቴሪያ መድሃኒቶችን እንደሚወስዱ የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል። በጥናቱ መሰረት በሀኪም ያልታዘዙ ጸረ ባክቴሪያ መድሃኒቶችን ማዝወተር መድሃኒቶችን የተላመዱ ቫክቴሪያዎች እንዲፈጠሩ ያደርጋል ተብሏል። መድሃኒቶቹ በሚወሰዱበት ጊዜም ‘‘ከፔኒሲሊዬም’’ ጀምሮ ደረጃ [...]]]>

ዓለም አቀፍ ደረጃ በርካታ ሰዎች ያለሀኪም ትዕዛዝ የጸረ ባክቴሪያ መድሃኒቶችን እንደሚወስዱ የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል።

በጥናቱ መሰረት በሀኪም ያልታዘዙ ጸረ ባክቴሪያ መድሃኒቶችን ማዝወተር መድሃኒቶችን የተላመዱ ቫክቴሪያዎች እንዲፈጠሩ ያደርጋል ተብሏል።

መድሃኒቶቹ በሚወሰዱበት ጊዜም ‘‘ከፔኒሲሊዬም’’ ጀምሮ ደረጃ በደረጃ መወሰድ ያለበት መሆኑን በሳለፍነው ዓመት የዓለም ጤና ድርጅት ይፋ መደረጉንም ዘገባው አስታውሷል።

ይሁን እንጂ አንዳንድ ሀገራት በቀጥታ ከከፍተኛ ምድሀኒቶች የሚጀምሩ መሆኑም ተጠቁሟል።

መድሀኒቶችን ያለሀኪም ትዕዛዝ አወሳሰዱ ተግባር ከቦታ ቦታ የሚለያይ መሆኑን የዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ያመለክታል።

በዓለም የጤና ድርጅት በ65 ሀገራት ላይ በተደረገ ክትትል ይፋ የተደረገው ሪፓርት መሰረት በኒዘርላንድ 9ነጥብ 78 በመቶ፣ ብሪታኒያ 38ነጥብ 18 ያህል ሰዎች ያለሀኪም ትዛዝ የጸረ ባክቴሪያ መድሃኒቶችን ተጠቃሚ መሆናቸው ለአብነት ተጠቅሰዋል።

ሞንጎሊያዎች ከላይ የተጠቀሱትን መድሃኒቶችን 64ነጥብ41 በመቶ በመጠቀም በዓለም አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያ ደረጃን ይዘዋል ተብሏል።

ጉዳዩ አፋጣኝ መፍትሄ እንደሚያስፈልገው የተገለጸ ሲሆን፥ በመድሃኒቶቹ አጠቃቀም ዙሪያ ጥብቅ ክትትል ማድረግ የሚጠይቅ መሆኑንም ነው ዘገባው የሚያመላክተው።

በሪፖርቱ ቡርንዲ በዝቅተኛ ደረጃ 4ነጥብ 44 በመቶ የመድሃኒቶች ተጠቃሚ መሆኗ የተገለጸ ሲሆን፥ የመድሃኒቶቹ አጠቃቀም ዝቅተኛ መሆን ደግሞ በቀላሉ ለመዳን የሚችሉ በሽታዎች እንዲባባሱ ያደርጋል ተብሏል።

ምንጭ: ኤፍ ቢ ሲ(FBC)

]]>
https://magazine.planetethiopia.com/2018/11/14/%e1%89%a0%e1%8b%93%e1%88%88%e1%88%9d-%e1%8a%a0%e1%89%80%e1%8d%8d-%e1%8b%b0%e1%88%a8%e1%8c%83-%e1%89%a0%e1%88%ad%e1%8a%ab%e1%89%b3-%e1%88%b0%e1%8b%8e%e1%89%bd-%e1%8b%ab%e1%88%88%e1%88%80%e1%8a%aa/feed/ 1
ታሪክን የኋሊት – ለ28 ዓመታት ጀርመንን ለሁለት ከፍሎ የነበረው የጀርመን ግምብ ሲፈርስ – 28 Years The Fall of Berlin Wall https://magazine.planetethiopia.com/2017/11/09/%e1%89%b3%e1%88%aa%e1%8a%ad%e1%8a%95-%e1%8b%a8%e1%8a%8b%e1%88%8a%e1%89%b5-%e1%88%8828-%e1%8b%93%e1%88%98%e1%89%b3%e1%89%b5-%e1%8c%80%e1%88%ad%e1%88%98%e1%8a%95%e1%8a%95-%e1%88%88%e1%88%81%e1%88%88/ Thu, 09 Nov 2017 13:58:47 +0000 http://www.planetethiopia.com/videos/articles/%e1%89%b3%e1%88%aa%e1%8a%ad%e1%8a%95-%e1%8b%a8%e1%8a%8b%e1%88%8a%e1%89%b5_1018.html                                                                       [...]]]>

                                                                          

                                                               
                                                   

የኔነህ ከበደ

የበርሊን ግምብ በፍልስፍናና በአስተዳደር ዘይቤ የአንድ አገር ሰዎችን ለሁለት በመክፈል የቀዝቃዛው ጦርነት ዘመን የጥላቻ ግድግዳ ተደርጐ ይቆጠራል፡፡

ለዓመታት ጀመርኖችን ከፋፍሎ የቆየው ግንብ ክፍት ሆኖ ምሥራቅ ጀርመናውያን ወደ ምዕራቡ እንዲሻገሩ የተፈቀደላቸው የዛሬ 28 ዓመት በዛሬዋ ዕለት ነበር፡፡

የጀርመን ናዚዎች ዓለምን በመዳፋችን ውስጥ እናውላለን ብለው ከ78 ዓመታት በፊት ጦርነት አቀጣጠሉ፡፡ የኋላ ኋላ በተነሱበት ፍጥነት መቀጠል ተሳናቸው፡፡

በሌሎች ላይ የለኮሱት እሳት ራሳቸውን ማቃጠሉን ያዘው፡፡

የህብረቱ ኃይሎች ከየአቅጣጫው መጡባቸው፡፡ የአንግሎ አሜሪካ ኃይል ከምዕራብ፤ የሩሲያ ሠራዊት ከምስራቅ አቅጣጫ መጡባቸው፡፡ መፈናፈኛ አጡ፡፡

አገራቸው በህብረቱ ኃይሎች ተፅዕኖ ስር ወደቀች፡፡

ከጦርነቱ በኋላ ምዕራባዊ ክፍሏ በአሜሪካ፣ እንግሊዝና ብሪታንያ አስተዳደር ስር ሆነ፡፡ 
የምስራቃዊው ክፍል ደግሞ በቀድሞዋ ሶቪየት ኅብረት ተፅዕኖ ሥር ወደቀ፡፡

ምዕራባዊው ክፍል የጀርመን ፌዴራል ሪፐብሊክ ተሠኝቶ ራሱን ቻለ፡፡ የምስራቁም ግዛት ምስራቅ በርሊንን ርዕሠ ከተማው በማድረግ በሶቪየት ተቀጥላነት የጀርመን ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ተባለ፡፡

በዚያን ጊዜው የሶቪየቶች መሪ ኒኪታ ኩርቺየቭ ቀጭን ትዕዛዝ ከግማሽ ምዕተ ዓመት በፊት በአንድ ሌሊት ምስራቅ በርሊን ዙሪያዋን በ155 ኪሎ ሜትር መጠነ ዙሪያ የማገጃ አጥር ተገጠገጠባት፡፡

የድንበር ጠባቂ ፖሊሶችም የተኩሰህ ግደል ፈቃድ ተሰጣቸው፡፡ በዘመኑ ግንቡን ዘለው ወደ ምዕራብ በርሊን ለመሻገር የሞከሩ ብዙዎች የአልሞ ተኳሾች ጥይት ዒላማ ሆነዋል፡፡

በዚህ አይነቱ ሙከራ የተገደሉት ከ200 እንደማያንሱ ይነገራል፡፡
                                               

በጊዜ ሂደት የሽቦ አጥሩ ከፍታ ጨምሮ ወደ ኮንክሪት ግንብነት ተለወጠ፡፡

ጊዜ አለፈ፡፡ 
ታሪክ እየተለወጠ መጣ፡፡

የቀድሞዋን ሶቪየት ኅብረት ጨምሮ በምስራቅና መካከለኛው አውሮፓ አገሮች የለውጥ ንፋስ መንፈስ ጀመረ፡፡

ያ የለውጥ ነፋስ ወደ ምስራቅ ጀርመንም ነፈሰ፡፡ 
ሕዝቡ እምቢ ለመብቴ ብሎ ተነሳ፡፡

አገዛዙ እንደ በፊቱ ሊያቆመው ሊቆጣጠረውና ሊያስታግሰው አልቻለም፡፡ 
የምስራቅ ጀርመን ሹሞች ሳይወዱ በግዳቸው የግንቡ ማገጃነት እንዲያበቃ ወሰኑ፡፡ 

ያሻው ሁሉ ወደ ምዕራብ በርሊን መሻገር ይችላል አሉ፡፡

አዋጁ እንደተሠማ በብዙ ሺህዎች የሚቆጠሩ ምስራቅ ጀርመናውያን ወደ ምዕራብ በርሊን ለመሻገር ወደዛው ተመሙ፡፡ የግንቡ መውጫ በሮች እንዲከፈቱላቸው ጠየቁ፡፡

አዋጁን ያላጣጣሙትና ግራ የተጋቡት የድንበር ጠባቂ ፖሊሶች አለቆቻቸውን ማብራሪያ መጠየቁን ተያያዙት፡፡ ግንቡን ክፍት አድርጉት ተባሉ፡፡ ሕዝቡ ጐርፍ ሆኖ ወደ ምዕራብ በርሊን ተመመ፡፡ ይሄ ከሆነ ዛሬ 28ኛ ዓመቱ ሆነ፡፡ የበርሊን ግምብ መውደቅ እንደ አገሪቱ ዳግም ውህደት ቀዳሚ ምልክት ተቆጠረ፡፡

ከጥቂት ዓመታት በኋላ የተነጣጠለችዋ ጀርመን ዳግም ተዋሐደች፡፡ 
የበርሊን ግምብ ፍርስራሽ ቅሪት የቀዝቃዛው ጦርነት ማክተም ተምሳሌታዊ ምልክት ተደርጐ ይታያል፡፡

ምንጭ:- የሸገር FM 102.1 ሬዲዮ

]]>