466 ሚሊየን ሰዎች የመስማት ችግር አለባቸው – የዓለም ጤና ድርጅት

woman listening to gossip

የዓለም ጤና ድርጅት በዓለም ዙሪያ 466 ሚሊየን ሰዎች የመስማት ችግር እንዳለባቸው ገለጸ።

ድርጅቱ ይህንን የገለጸው በትናትናው ዕለት የመስማት ቀንን አስመልከቶ በጉዳየ ዙሪያ የሚነሱ ችግሮችን መቅረፍ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ባካሄደበት ወቅት ነው።

ድርጅቱ በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2050 የመስማት ችግር ያለባቸው ሰዎች አሁን ከተገለጸው ቁጥር በእጥፍ ሊጨምር እንደሚችል ስጋቱን ገልጿል።

ይህንን ለመከላከልም በሞባይል ስልክና ድረ ገጽን መሰረት ያደረገ ‘ሂርሁ’  ”hearWHO” የተሰኘ መተግበሪያ ይፋ አድርጓል።

መተግበሪያው ሰዎች በቀላሉ ጆሮዋቸው በትክክል ስራውን እየሰራ ስለመሆኑ እንዲያረጋግጡ ይረዳል ብለዋል።

የጤና ሰራተኞችም በቀላሉ መተግበሪያው የሰዎችን ጤንነት እንዲከታተሉ እንደሚረዳም ተገልጿል።

የድርጅቱ ቴክኒካል ኦፊሰር እንደገለጹት ሰዎች በተፈጥሮ የተሰጣቸውን የመስማት ክህሎት አንድ ጊዜ የሚያጡ ከሆነ ወደ መጀመሪያው መመለስ አስቸጋሪ መሆኑን ጠቅሰው ሰዎች በየጊዜው የጆሮዋቸውን ጤንነት እንዲከታተሉ አሳስበዋል።

ምንጭ: ኤፍ ቢ ሲ(FBC)

Advertisement

2 Comments

Comments are closed.