‹‹ግጭት ተኮር የቪዲዮ ጨዋታዎችን ማየት የሚያዘወትሩ ታዳጊዎች በማህበራዊ የህይወት መስተጋብራቸው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ይደርስባቸዋል፡፡›› ጥናት

ግጭት ተኮር የቪዲዮ ጨዋታዎችን ማየት የሚያዘወትሩ ወጣቶች ማየት ከማያዘወትሩት የበለጠ በማህበራዊ የህይወት መስተጋብራቸው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚደርስባቸው ያስነበበው ሳይንስ ደይሊ ነው፡፡

ጥናቱን ያረጋገጡት በሀገረ እንግሊዝ በሚገኘው ዳርት ማውዝ ዩኒቨርሲቲ ሳይንቲስቶች ናቸው፡፡ ሳይንቲስቶቹ አስፈሪ፣ተንኮል ተኮር፣በይበልጥ የግጭት ይዘት ወይም ሴራ እና የድብድብ ፊልሞችን አዘውትረው በሚመለከቱ በጉልምስና የእድሜ ክልል በሚገኙ ወጣቶች ዙሪያ ነው ጥናታቸውን ያከናወኑት፡፡
በእንደዚህ አይነት የፊልም ዘውጎች የተለከፉ ታዳጊዎች ከሌሎቹ አቻወቻቸው በተለዩ ቁጡ እና ጠብ ጫሪዎች የመሆን ዕድላቸው ከፍተኛ ነው ሲሉ አረጋግጠዋል፡፡

ጥናት አድራጊዎቹ በጉዳዩ ዙሪያ 17ሺህ ወካይ ታዳጊዎችን አሳትፈዋል፡፡ ከበርካታ ሀገራት የተወጣጡ እድሜያቸው ከ9 እስከ 19 የሆኑ ግለሰቦችም ተሳታፊ እንደሆኑ ተጠቁሟል፡፡አስፈሪ ወይም የጭካኔ ፊልሞችን አዘውትረው የሚመለከቱት ወይም የሚጫወቱ የጥናቱ ተሳታፊዎች ከማይመለከቱት አቻወቻቸው የበለጠ ፀብ ጫሪዎች፣በቤተሰቦቻቸው፣በአስተማሪዎቻቸው እና በእድሜ ከሚበልጧቸው ሰዎች እንኳን ሳይቀር የሚጋጩ መሆናቸውን አረጋግጠናል ነው ያሉት፡፡

ጥናቱ በትክክል ዕውን መሆኑን ለማረጋገጥ ከ24 ጊዜ በላይ የተለያዩ ተሳታፊዎች እንደተካተቱበት ተጠቁሟል፡፡ ከአካላዊ ጉዳቱ በተጨማሪም ለስነ-ልቦና ጉዳት እንደሚዳርግ ተጠቁሟል፡፡

ምንጭ:  Amhara Mass Media Agency

Advertisement

3 Comments

Comments are closed.