ሞሮኮ የገነባችውን በአፍሪካ ፈጣኑን የባቡር መስመር በዚህ ሳምንት መሞከር ጀምራለች

                                                                   

ሞሮኮ ገንብታ ያጠናቀቀችውን በአፍሪካ ፈጣን የተባለውን የባቡር መስመር መሞከር ጀመረች።

ባቡሩ በሰዓት 320 ኪሎ ሜትር የሚጓዝ ነው።

የባቡር መስመሩ ላይ ሰኞ እለት በተደረገ የሙከራ ጉዞ ባቡሩ በሰዓት 275 ኪሎ ሜትር ተጉዟል።

ይህ ባቡር በካዛብላንካና ታንገርስ መካከል ይወስድ የነበረውን ሰዓት በሁለት ሶስተኛ የሚቀንስ ነው።

ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 2 ነጥብ 4 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ወጪ የተደረገበት ሲሆን፥ 50 በመቶውን ወጪ አገሪቱ የሸፈነችው ከፈረንሳይ ባገኘችው ብድር ነው።

በፈረንሳይ ኩባንያ የተገነባው ይህ የባቡር መስመር ሙሉ በሙሉ የሙከራ ጊዜውን አጠናቆ ወደ ስራ የሚገባው በፈረንጆቹ 2018 ነው ተብሏል።

የሞሮኮ መንግስት በዓመት 6 ሚሊየን ሰዎችን የማመላለስ አቅም ያለው የባቡር መስመሩ መዘርጋት የአገሪቱን የመሰረተ ልማት የሚያዘምን መሆኑን ተገልጿል።

ምንጭ:- ኤፍ ቢ ሲ(FBC)

Advertisement