የህፃናትን ሰውነት ማሻሸት በሽታን ያስታግስላቸዋል

የህጻናትን ሰውነት በዝግታ ማሻሸት በአእምሯቸው ውስጥ ከህመም ጋር ተያይዞ ያለውን ስራ በማቅለል ከህመም ስሜት እንደሚያስታግስ አዲስ የተሰራ ጥናት አመልክቷል።

በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ እና በሊቨርፑል ጆን ሞርስ ዩኒቨርሲቲ በጋራ የተሰራው ጥናቱ የ32 ህጻናት የደም ምርመራ በሚያደርጉበት ጊዜ የአእምሯቸውን እንቅስቃሴ ተመልክቷል።

በዚህ ወቅትም ግማሽ ያክሉ ህጻናት ልስላሴ ባለው ብሩሽ ሰውነታቸው እንዲዳበስ የተደረገ ሲሆን፥ በዚህም በአእምሯቸው ውስጥ የሚፈጠር የህመም እንቅስቃሴን በ40 በመቶ መቀነሱ በጥናቱ ተመልክቷል።

እንደ ተመራማሪዎቹ ገለፃ፥ ህጻናትን በጣም በዝግታ ሰውነታቸውን ማሻሸት በአእምሯቸው ውስጥ ያለውን የስራ ጫና ይቀንሳል።

ወላጆች ህጻናት ልጆቻቸውን ሰውነት ቢያሻሹ በተለይም በሆዳቸው እንዲተኙ በማድረግ ጀርባቸው ላይ በጣም በዝግታ እና ልስላሴ ባለው መልኩ ማሻሸትን ቢያዘወትሩ ጠቀሜታው ከፍተኛ መሆኑን ተመራመኛሪዎቹ ጠቁመዋል።

ከዚህ በፊት በተሰራ ጥናትም የህፃናትን ሰውነት መነካካት እና ማሻሸት ከቤተሰባቸው ጋር ያላቸውን ግንኙነል ለማጠናከር፣ የህጻናቱን እና የቤተሰብን ጭንቀት ለመቀነስ እንዲሁም ህፃን ልጅ በአጋጣሙ ታሞ ወደ ሆስፒታል ካለ በፍጥት እንዲወጣ ያስችላል።

ምንጭ: ኤፍ ቢ ሲ (FBC)

Advertisement

8 Comments

  1. Very good article! We are linking to this particularly great content on our site. Keep up the great writing.

Comments are closed.