መስቀል በቤተ-ጉራጌ – Mesqel Celebration in Bete Gurage

የጉራጌ ብሄር ተወላጆች ለመስቀል ወደትውልድ ቀያቸው ያመራሉImage copyright ASHENAFI TESFAYE
አጭር የምስል መግለጫ የጉራጌ ብሄር ተወላጆች ለመስቀል ወደትውልድ ቀያቸው ያመራሉ

በቤተ- ጉራጌ መስቀል የአንድ ቀን በዓል አይደለም፡፡ ከ10 ቀናት በላይ የሚወስድ ልዩ የፈንጠዝያ ረድፍ እንጂ፡፡

ከመስከረም 12 በፊት የጉራጌ ብሄር ተወላጆች፤ ከመላው የሀገሪቱ ክፍል ወደ ትውልድ ስፍራቸው ይተማሉ፡፡

የዕድሜ ባለጸጋው አቶ ፍቃዱ ካሶሬ እንደሚያምኑት፤ ከወጣቶች በሰው እስከሚደገፉ አዛውንቶች ድረስ የመስቀል ሰሞን ሀገር ቤት የመግባታቸው ነገር አያጠያቅም፡፡ በዚያ ሰሞን በጉራጌዎች የንግድ ተሳትፎ ፈክታ የከረመችው አዲስ አበባ ጭርታ ይመታታል፡፡

‹‹አሁን በዚህ ሰሞን መርካቶ ብትሄድ፣ የተወረረ ቦታ መስሎ ታገኘዋለህ›› ይላሉ እሳቸው ሁኔታውን ሲስሉት፡፡

ልጃቸው መሳይ ፈቃዱን ጨምሮ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የብሄረሰቡ ተወላጆች ወደ ቀያቸው አቅንተዋል፡፡ ምክንያቱም መስቀል በጉራጌ ሃይማኖታዊ በዓል፣ የመተጫጫ ወቅት፣ የእርቅ እና የአንድነት አውድ ስለሆነ በመሳይ አገላለጽ ‹‹መች በደረሰ የሚያስብል ወቅት›› ነውና፡፡

ከወሬት ያህናእስከ አዳብና

አቶ ፈቃዱ ካሶሬ እንዳወጉን፤ መስከረም 13 ወሬት ያህና በተሰኘው የበዓል መክፈቻ መሰናዶ ሰሞነ መስቀል ይጀመራል፡፡ ወሬት ያህና ጉጉት እና ናፍቆት የፈጠረውን እንቅልፍ አልባ ቀን የሚዘክር ቃል ነው፡፡

መስከረም 14 የእርድ ዋዜማ ሲሆን የልጆች የደመራ ፣ የሴቶች የአይቤ እና ጎመን ቀን ይባላል፡፡ ቤቶች የሚሰነዳዱበት የእንፋሎት ቆጮ የሚቀርብበት ቀንም ነው፡፡

መስከረም 15 ዋናው የጉራጌ የመስቀል በዓል (ወኀምያ ) ነው፡፡ በዚህ ዕለት እርድ ይፈጸማል፡፡ መስከረም 16 ምግይር ወይም ደመራ የሚባለው ቀን ነው (የአባቶች ደመራም ይባላል)፡፡

በየቤቱ፤ ጠዋት የህጻናት ማታ ደግሞ የአባቶች ደመራ ይለኮሳል፡፡ በዚህ ዕለት ከብቶች ከቤት አይወጡም፡፡

በዋናው በዓል እርድ ይፈጸማልImage copyright ASHENAFI TESFAYE
አጭር የምስል መግለጫ በዋናው በዓል እርድ ይፈጸማል

መስከረም 17 ንቅባር ወይንም ትልቁ በዓል ነው፡፡ ዘመድ አዝማድ ሻኛ አስመርቆ በጋራ የሚቋደስበት፣ ጎረቤት በአንድ ሆኖ ሲስቅ ሲያወካ የሚውልበት የማህበረሰብ መሰብሰቢያ ቀን ነው፡፡

ከመስከረም 18 እስከ 23 የጀውጀው የሚባለው ስርዓት ይቀጥላል፡፡ የጀውጀው የመተያያ ቀን ሲሆን ባለትዳሮች ስጦታ እና መመረቂያ ይዘው የወላጆቻቸውን ቤት በማቅናት የሚጠይቁበት ነው፡፡

የመዝጊው በዓል አዳብና ይባላል፡፡ አዳብና ጎረምሶች እና ልጃገረዶች የጭፈራ ችሎታቸውን የሚያሳዩበት፤ የወደፊት የትዳር ተጣማሪያቸውን የሚያዩበት፣ የሚያጩበት በዓል ነው፡፡ ጭፈራው ለተወሰኑ ቀናትን ሊቀጥል ይችላል፡፡

የአቶ ፈቃዱ ካሶሪ ልጅ፤ ባህሉ በሚፈቅደው መንገድ ካጨና ካገባ ዘንድሮ አንድ ዓመት እንደደፈነ ይናገራል፡፡ እንግዲህ መስቀል በሚመጣ ጊዜ ‹‹ለእኔ ድርብ በዓል ነው›› ብሎናል፡፡

የዓመት ሰው ይበለን

ወደ ሁለት ሚሊየን የሚገመቱ የብሄረሰቡ አባላት እንደሚሳተፉበት የሚነገረው በዓል የሚያካትታቸው ክንውኖች ካለ ምርቃት እና መልካም ምኞቶች አይደመደሙም፡፡

የዕድሜ ባለጸጎች ‹‹የሀገራችንን ዳር ዳር ለጠላት እሳት፤ ለህዝቦቿ መሃሏን ገነት ያድርግልን›› ከሚለው ምርቃት ጀምሮ፤ ሰው፣ ከብቱ፣ ጋራ እና ሸንተረሩ ሰላም እና ልምላሜ፣ በረከት እና ጸጋ እንዳይለየው ይመረቃል፡፡

ታዳሚውም የአባቶችን ምርቃት እየተከተለ ‹‹አሜን!›› ይላል፡፡ የዓመት ሰው ይበለን- አሜን!

ምንጭ: ቢቢሲ

Advertisement

39 Comments

  1. Aw, this was a really nice post. In thought I would like to put in writing like this moreover ?taking time and precise effort to make a very good article?but what can I say?I procrastinate alot and not at all seem to get something done.

  2. You made some respectable points there. I regarded on the internet for the issue and found most individuals will associate with along with your website.

  3. That is the proper weblog for anybody who wants to find out about this topic. You realize a lot its virtually laborious to argue with you (not that I actually would want匟aHa). You positively put a new spin on a subject thats been written about for years. Nice stuff, just great!

  4. Can I simply say what a reduction to seek out someone who truly is aware of what theyre talking about on the internet. You definitely know how one can convey a problem to mild and make it important. Extra folks must read this and understand this side of the story. I cant consider youre no more fashionable because you positively have the gift.

  5. There are certainly a whole lot of particulars like that to take into consideration. That is a nice level to deliver up. I offer the thoughts above as common inspiration however clearly there are questions just like the one you bring up the place crucial factor can be working in trustworthy good faith. I don?t know if finest practices have emerged round things like that, however I’m positive that your job is clearly identified as a good game. Both boys and girls really feel the affect of only a second抯 pleasure, for the remainder of their lives.

  6. I discovered your blog website on google and test a couple of of your early posts. Continue to keep up the excellent operate. I just extra up your RSS feed to my MSN Information Reader. In search of forward to reading extra from you later on!?

  7. Oh my goodness! a tremendous article dude. Thanks However I am experiencing situation with ur rss . Don抰 know why Unable to subscribe to it. Is there anyone getting equivalent rss downside? Anyone who knows kindly respond. Thnkx

Comments are closed.