ጎዳና ተዳዳሪዎችን በህክምና መታደግ

መኮንን ገብረመድህን ጅግጅጋ ይኖር ነበር። በጅግጅጋ የተቀሰቀሰው አለመረጋጋት ግን ቤት ንብረቱን ጥሎ ወደ አዲስ አበባ እንዲሸሽ አስገድዶታል። አዲስ አበባ መስቀል አደባባይ አካባቢ ጎዳና ላይ ከወደቀ ስድስት ቀናት ተቆጥረዋል።

መኮንን ለሁለት ዓመት ያህል አይኑን ይጋርደው ነበር። ለጎዳና ተዳዳሪዎች ነጻ ህክምና እንደሚሰጥ ሲሰማ እድሉን ለመጠቀም ህክምናው ወደሚሰጥበት ቦታ አቀና።

“ስለ ጤና ችግሬ ስነግራቸው ካርድ አወጡልኝና ጳውሎስ፣ ራስ ደስታ ወይም ሚኒሊክ ሄደህ በነጻ መታከም ትችላለህ አሉኝ” ይላል።

• ጤና የራቀው የፈለገ ህይወት ሆስፒታል

• ትዳር ከባድ የጤና ችግሮችን ለመከላከል

ይህ ለመኮንን መልካም ዜና ነው። የጎዳና ተዳዳሪዎችን ህይወት ፈታኝ ከሚያደርጉ እውነታዎች አንዱ የህክምና አገልግሎት ለማግኘት አለመቻላቸው ሲሆን፤ ይህንን ከግምት በማስገባት ነሀሴ 16፣ 2010 ዓ. ም. መስቀል አደባባይ አካባቢ ነጻ የህክምና አገልግሎት ተሰጥቷል።

የህክምና አገልግሎት የመስጠት ሀሳቡ ጠንሳሾች ‘ዘመን’ የተሰኘው የቴሌቭዥን ተከታታይ ድራማ አዘጋጆችና ተዋንያን እንዲሁም የጤና ጥበቃ ሚንስትር ናቸው።

የ’ዘመን’ ድራማ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ደረጀ አርአያን ያገኘነው የጎዳና ተዳዳሪዎች ህክምናውን እንዲያገኙ ቅስቀሳ በማድረግ ህክምናው ወደሚሰጥበት ቦታ ሲወስድ ነበር።

በየአካባቢው የሚገኙ የጎዳና ተዳዳሪዎች ህክምናው ወደሚሰጥበት ቦታ ሄደው የህክምና ካርድ እንዲያገኙ ማሳመን ቀላል እንዳልነበርም ተገልጿል።

አዲስ አበባ ውስጥ ለሚኖሩ የጎዳና ተዳዳሪዎች 1000 የህከምና ካርዶች ተዘጋጅተዋል።

በካርዱ ነጻ ህክምና ከማግኘታቸው በተጨማሪ መድሀኒትም በነጻ ይሰጣቸዋል።

ሀምሌ 16 የነበረው ነጻ የህክምና አገልግሎት ውስጥ ሴተኛ አዳሪዎችም ተካተው ነበር። እስከ እኩለ ለሊት ድረስ በተንቀሳቃሽ መኪና ባሉበት ቦታ ሆነው ህክምና እንዲያገኙ ተደርጓል።

በተንቀሳቃሽ አምቡላንሶችም አገልግሎት ተሰጥቷል
አጭር የምስል መግለጫበተንቀሳቃሽ አምቡላንሶችም አገልግሎት ተሰጥቷል

ደረጀና የተቀሩት የድራማው አዘጋጆችና ተዋንያን በጤናው ዘርፍ በጎ አገልግሎት መስጠት የጀመሩት ሀምሌ 16፣ 2010 ዓ. ም. ነበር።

ሰኔ 16 መስቀል አደባባይ የደረሰውን የቦንብ ፍንዳታ ተከትሎ ተጎጂዎችንና ሌሎችም ህሙማንን በመጠየቅ፣ ሆስፒታሎችን በማጽዳት የበኩላቸው አስተዋጽኦ አበርክተዋል።

ይህንን ባደረጉበት በወሩ ለጎዳና ተዳዳሪዎች የነጻ ህክምና በመስጠት ተሳትፎ አድርገዋል።

“የበጎ ፍቃድ አገልግሎት እንዲለመድ እንፈልጋለን፤ ስለዚህ በየወሩ 16ኛው ቀን ላይ በተለያየ ዘርፍ አገልግሎት እንሰጣለን” ይላል።

በሚቀጥለው ወር ከግብረ ሰናይ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ለጎዳና ተዳዳሪዎች የሚሆን ገንዘብ የሚሰባሰብበት የእራት መርሀ ግብር ለማዘጋጀት አስበዋል። በቀጣይ ወራት የትራፊክ አደጋን በመቀነስና በሌላም መንገድ እንደሚሳተፉ ተናግሯል።

ለጎዳና ተዳዳሪዎቹ ህክምና ስትሰጥ ያገኘናት ዶክተር ማህሌት ብርሀኑ የጳውሎስ ሆስፒታል ሰራተኛ ናት።

በመስቀል አደባባይ አስር ሀኪሞችን ጨምሮ፣ ነርሶች፣ የላብራቶሪ ቴክኒሺያኖች መገኘታቸውን ትናገራለች። ተንቀሳቃሽ አንቡላንስም በቦታው ተገኝቷል።

የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ ከመስጠት ባሻገር ተጨማሪ ህክምና ለሚያስፈልጋቸው ሪፈር ጽፈዋል።

ጳውሎስ፣ ጴጥሮስ፣ ሚኒሊክ፣ አለርትና የካቲት 12 የጎዳና ተዳዳሪዎቹ በነጻ ህክምና ማግኘት ከሚችሉባቸው ሆስፒታሎች መካከል ይጠቀሳሉ።

የነጻ ህክምና ካርድ ተሰጥቷቸዋል
አጭር የምስል መግለጫየነጻ ህክምና ካርድ ተሰጥቷቸዋል

ዶክተር ማህሌት እንደምትለው፤ የጎዳና ተዳዳሪዎች የጤና እክል ሲገጥማቸው ወደ ህክምና መስጫ ሄደው በነጻ መታከም እንደሚችሉ ግንዛቤ ማስጨበጥ ከግቦቻቸው አንዱ ነው።

እሷ ህክምና ከሰጠቻቸው መካከል ለዓመታት ህክምና ያላገኙ ግለሰቦች ይገኙበታል።

“መታከም ብዙ ወጪ ይጠይቃል። መድሀኒትም ውድ ነው ብለው በማሰብ ህመማቸውን ችለው የሚኖሩ ብዙ ናቸው። የነጻ ህክምና ካርድ ካላቸው ግን በማንኛውም ሰአት መታከም ይችላሉ” ትላለች።

“የዋስትና ካርድ” ብላ የምትጠራውን የነጻ ህክምና ካርድ የያዙ የጎዳና ተዳዳሪዎች ድንገተኛ አደጋ ሲገጥማቸውም በቀላሉ ህክምና ማግኘት ይችላሉ።

ምንጭ: ቢቢሲ

Advertisement

25 Comments

  1. Having read this I believed it was very enlightening.
    I appreciate you finding the time and energy to put this information together.
    I once again find myself spending a lot of time both reading and
    leaving comments. But so what, it was still worth it!

  2. Please let me know if you’re looking for a article writer for
    your blog. You have some really great posts and I think I would
    be a good asset. If you ever want to take some of the load
    off, I’d really like to write some articles for your blog in exchange
    for a link back to mine. Please blast me an e-mail if interested.

    Thank you!

  3. Write more, thats all I have to say. Literally,
    it seems as though you relied on the video to make your point.

    You clearly know what youre talking about, why throw away your
    intelligence on just posting videos to your blog when you could be giving
    us something enlightening to read? 32hvAj4 cheap flights

  4. I’m no longer sure the place you’re getting your info, however good
    topic. I needs to spend some time learning more or understanding more.
    Thank you for fantastic info I was searching for this info for
    my mission. yynxznuh cheap flights

  5. This is the right blog for anybody who would like to understand this topic.
    You realize a whole lot its almost hard to argue with you (not that I
    personally will need to…HaHa). You certainly put a fresh spin on a subject that’s been written about for years.
    Excellent stuff, just excellent!

  6. My brother recommended I may like this web site. He was entirely right.
    This post actually made my day. You cann’t consider simply
    how a lot time I had spent for this info! Thank you!

  7. Howdy, i read your blog occasionally and i own a similar one and i
    was just wondering if you get a lot of spam responses?
    If so how do you stop it, any plugin or anything you can advise?
    I get so much lately it’s driving me insane so any help is very
    much appreciated.

  8. Currently it appears like BlogEngine is the top blogging platform out there right now.
    (from what I’ve read) Is that what you are using on your blog?

  9. You could certainly see your skills within the article you write.
    The sector hopes for even more passionate writers such as you who aren’t
    afraid to say how they believe. At all times go after your heart.

  10. Have you ever thought about publishing an e-book or guest authoring on other blogs?
    I have a blog centered on the same subjects you
    discuss and would really like to have you share some stories/information. I know my subscribers would appreciate your work.
    If you’re even remotely interested, feel free to
    shoot me an e-mail.

Comments are closed.