ሀሰተኛ የከንፈር ውበት መጠበቂያ ቀለሞች ለከፋ የጤና ጉዳት ስለሚያስከትሉ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል

                                                           

የትክክለኛነት ማረጋገጫ የሌላቸው ሀሰተኛ የከንፈር ውበት መጠበቂያ ቀለሞችን መጠቀም ለከፋ የጤና ጉዳት እንደሚያጋልጥ ተነግሯል።

በብሪታኒያ ፓርላማ የሰብዓዊ እና ማህበራዊ ደህንነት ጉዳዮች ኮሚቴ ሀሰተኛ የከንፈር ውበት መጠበቂያ ቀለሞች ከጤና ጥበቃ መመሪያ ውጭ የሆኑ እና ከፍተኛ ጉዳት እንደሚያደርሱ በክትትል ደርሼበታለሁ ብሏል።

በፌስቡክ እና በኢ-ቤይ አማካኝነት ለ300 ደንበኞች ሀሰተኛ ምርቶችን የሸጠ ግለሰብም ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት አምርቶ በእስራት እንዲቀጣ ተደርጓል።

ሀሰተኛ የከንፈር ውብት መጠበቂያ ቀለሞችን በመደበኛ ሁኔታ የሚጠቀሙ ከሆነ፥ ለከፍተኛ የደም ግፊት፣ ለመራቢያ አካል ችግር፣ ለአዕምሮ እና ለልብ ህመም ያጋልጣል ነው የተባለው።

በተለይም ነፍሰጡር ሴቶች ቀለሞቹን በሚጠቀሟቸው ጊዜ በማህፀን ውስጥ ላሉ ህፃናት የአዕምሮ ህዋሳት መውደም ይዳርጋል።

ሀሰተኛ ምርቶችን ገዝተው የሚጠቀሙ ሰዎች የከፋ የጤና ጉዳት ሳይደርስባቸው በፊት ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው ተብሏል።

በመሆኑም በየመንገዱ ወይም በማንኛውም ሱቅ በቅናሽ ዋጋ ያለማብራሪያ እና ያልምንም የትክክለኝነት ማረጋገጫ የሚሸጡ የከንፈር ማስዋቢያዎችን ከመግዛት መቆጠብ እንዲያስፈልግ ተመክሯል።

በተለይም የከንፈር ውበት መጠበቂያ ቀለሞችን መጠቀም የሚፈልግ ሰው ካለ ወደ ኮስሞቲክስ ሱቆች ወይም መድሃኒት ቤቶች ጎራ በማለት ማማከር እና የሚያስፈልገውን ምርት መግዛት እና በአጠቃቀሙ መሰረት መጠቀም ይግባል ነው የተባለው።

የንግድ እና የጤና ተቋማትም ሀሰተኛ የከንፈር ውበት መጠበቂያ በሚሸጡ ሰዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር መስራት እና የግንዛቤ በቀለሞቹ ጉዳት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን መስራት እንንዳለባቸውም ተመክሯል።

ምንጭ:- ኤፍ ቢ ሲ(FBC)

Advertisement