ጭንቀት አእምሯችንና ሰውነታችን ላይ ምን አይነት ችግር ይፈጠራል…?

                                             

ጭንቀት የህይወት ውጣ ውረድ ውስጥ የሚያጋጥም ሲሆን፥ በርካቶቻችንም በተለያዩ ጊዜያት ተጨንቀን እንደምናውቅ እውን ነው።

ጭንቀት በርካታ መንስኤዎች ሲኖሩት፥ ከምንኖርበት አካባቢ፣ ከሰውነታችን፣ ከምንናገረው ነገር እና ለምንኖርበት ዓለም ያለን አተያይ ጋር ተያይዞ ሊከሰት ይችላል።

እንደ ፈተና ያሉ ነገሮች በሚያጋጥሙን ጊዜ ጭንቀት ተፈጥሯዊ ነገር ሲሆን፥ ሆኖም ግን በስነ ልቦናችን ጭንቀቱን የመቋቋም እና ምላሽ የመስጠት አቅምን ተፈጥሮ ለግሳናለች።

ጫና ውስጥ ገብተን የጭንቀት ስሜት በሚሰማን ጊዜ የነርቭ ስርዓታችን ሰውነታችን የጭንቀት ሆርሞን የሆኑትን “አድሬናይል፣ ኖራድሬላይን እና ኮርቲሶል” እንዲለቅ ትእዛዝ ያስተላልፍለታል።

ይህም ስነ ልቦናዊ ለውጥ እንዲመጣ በማድረግ በጭንቀት ምክንያት ሊከሰትብን የሚችለውን ጉዳት ለመመከት የሚያስችል ሲሆን፥ “የጭንቀት ምላሽ” ተብሎ ይነገራል። 

ለጭንቀት ምላሽ የሚሰጠው የአካላችን ክፍል ሁሌም ንቁ ከሆነ፥ ጭንቀት ለምንሰራው ስራ ትኩረት እንድንሰጥ እና በተነሳሽነት እንድነሰራ ስለሚያደርግ ጠቀሜታ እንዳለው ይነገራል።

ጭንቀት በሰውነታችን ላይ የሚያስከትለው የጤና እክል…

ጭንቀት በተደጋጋሚ የሚከሰትብን ከሆነ እና ስሜቱ ለረጅም ሰዓት የሚቆየበን ከሆነ ወይም ደግሞ መጥፎ የሆነውን ስሜት ሰውነታችን መቆጣጣር ካቃጠው በዚህ ጊዜ ችግር እንደሚፈጠር ይነገራል።

የነርቭ ስርዓታችን ለተከሰተብን የጭንቀት ስሜት ምላሽ መለቆጣጠር በሚል በተከታታይነት ምላሽ በሚሰጥበት ጊዜ ከፍተኛ ላብ ሰውነታችንን ሊያጠምቅ ይችላል።

የመተንፈሻ አካል ላይ ጉዳት ያስከትላል፦ አብዝተን ስንጨነቅ ጠንከር ያለ እና ፍጥነት የተሞላበት አተነፋፈስ ይስተዋልብናል፤ ይህም ኦክሲጅን በብዛት እና በፍጥነት በደማችን ውስጥ እንዲሰራጭ ያደርጋል ተብሏል።

ከዚህም በላይ እንደ አስም ያሉ የመተንፈሻ አካል የጤና እክል ላላቸው ሰዎች ላይም ጭንቀት የበለጠ ጉዳት ያስከትላል ነው የተባለው።

የሰውነትን በሽታ የመከላከል አቅምን ያዳክማል፦ አብዝተን በምጨነቅበት ጊዜ የነርቭ ስርአታችን ጭንቀቱን ለመቆጣጣር የሚለቀው ኮርቲሶል የተባለ ሆርሚን የሰውነታችን በሽታ የመከላከል እቅም ላይ ጫና ያሳድራል።

በዚህ ጊዜም ለኢንፌክሽኖች እና ለሌሎች የበሽታ አይነቶች የመጋለጥ እድላቸውን የሚጨምር ሲሆን፥ ሰውነታችን በሽታን ለመከላከል የሚያደርገው ጥረትም ይዳከማል ነው የተባለው።

የልብ ጤንነት ላይ ችግር ያስከትላል፦ ጭንቀት በበዛ ቁጥር የልባችን ጤንነት ላይ እከል እንደሚፈጥርም ተነግሯል።

የጭንቀት ስሜት በሚሰማን ጊዜ የልብ ምታችን እና የደማችን ዝውውር ፍጥነት የሚጨምር ሲሆን፥ ጭንቀቱ በሚወገድልን ጊዜ ሁሉም ወደ ነበረበት ቦታ ይመለሳል።

ሆኖም ግን ጭንቀቱ በዘላቂነት ለረጀም ጊዜ የሚቆይብን ከሆነ የደም ቧንቧዎቻችን ላይ ጎዳት የሚያስከትል ሲሆን፥ይህም ለድንገተኛ የልብ ህመም፣ ለከፍተኛ የደም ግፊት እና ለስትሮክ የመጋለጥ እድላችንን ከፍ ያደርገዋል ተብሏል።

የጨጓራ ህመም ሊያስከትል ይችላል፦ አብዝቶ መጨነት ለጨጓራ ህመም ሊዳርገን እንደሚችለም ተነግሯል።

የመራቢያ ስርዓት ላይ እክል ይፈጥራል፦ አብዝቶ መጨነቅ ወንዶች ላይ የቴስቴስትሮን እና የወንድ ዘረ የማመንጨት ሂደትን ይጎዳል የተባለ ሲሆን፥ እንዲሁም ስንፈተ ወሲብ እና የብልት አለመቆምን ሊያስከትል እንደሚችልም ይነገራል።

ጭንቀት በሴቶች ላይም የወር አበባ ኡደትን እንዲዛባ ያደርጋል የተባለ ሲሆን፥ የወር አበባ በሚመጣ ጊዜ የሚሰሙ የህመም ስሜቶች እንዲጨምሩ ያድረጋልም ተብሏል።

ጭንቀት እና አእምሯችን…

አብዝቶ መጨነቅ “ሀይሬራሮዡዋል” የተባለ እክል ሊያስከትልብን የሚችል ሲሆን፥ ይህም እንቅልፍ ቶሎ አለመተኛት፣ ለረጅም ሰዓት መተኛት አለመቻል እና በድካም የተሞላ ምሽትን ማሳለፍ ነው።

ይህም ነገሮች ላይ ትኩረት የመስጠት፣ የመማር እና የማስታወስ አቅማችን ላይ ችግር ሊፈጥር እንደሚችል ነው የተነገረው። 

ምንጭ:- ኤፍ ቢ ሲ(FBC)

Advertisement